ቢዝነስ

በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የፀሐይ ኃይልን ለምግብ ማብሰያነት የሚያገለግል ማሽን ተሰራ

By Feven Bishaw

August 01, 2022

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የመሠረታዊ ምህንድስና ሳይንስ ምርምርና ፈጠራ ማዕከል የፀሐይ ኃይልን ለምግብ ማብሰያነት የሚያገለግል ማሽንና ከወዳደቁ የውሃ ማሸጊያ ፕላሰቲኮች የእግረኛ መንገድ ኮምፖሲት ምንጣፍ ተሰራ፡፡

የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ ኪሎሌ ተስፋዬ እንደገለፁት÷ በተመራማሪ ዶክተር አምባቸው ማሩ እና አቶ አበበ ኃይሌ የተሰራው የፀሐይ ኃይልን ወደ ኢነርጂ ኃይል የሚቀይር ሲስተም የተፈጠረው ለምግብ ማብሳያነት የሚውል ማሽን ነው።