Fana: At a Speed of Life!

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ለ2015 በጀት አመት ከ3 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ አፀደቀ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 27 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ባካሄደው 6ኛ ዙር 1 አመት 2 መደበኛ ጉባኤ 3 ቢሊየን 405 ሚሊየን 105 ሺህ ብር ሆኖ የቀረበለትን የክልሉ መንግስት የ2015 በጀት አፅድቋል።

የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ምክትል ኃላፊ አብዱልባሲጥ አቡበከር ከተያዘው በጀት 51 በመቶ ለካፒታል በጀት እንዲሁም 49 በመቶው ደግሞ ለመደበኛ በጀት የሚውል ነው ብለዋል።

በጀቱም በዋናነት በክልሉ ከተለያዩ ገቢዎች ከሚሰበሰብ ገቢ እና ከፌዴራል መንግስት ድጎማ የሚሸፈን መሆኑን ተናግረዋል።

የፀደቀው በጀት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ14 በመቶ ብልጫ እንዳለው መገለጹን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.