የሀገር ውስጥ ዜና

ልማት ባንክ በተጠናቀቀው በጀት አመት 11 ቢሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ከሰጠው ብድር ሰበሰበ

By Feven Bishaw

August 07, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በተጠናቀቀው 2014 በጀት አመት 10 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ከሰጠው ብድር መሰብሰብ መቻሉን ገለፀ።

ባንኩ የትግራይ ክልል ፕሮጀክቶችን ሳይጨምር የተበላሸ ብድር ደረጃን ወደ 17 በመቶ ማውረድ መቻሉንም አስታውቋል።