የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲስ አበባ ከታሪፍ ጋር በተያያዘ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ያለመ ምክክር ተደረገ

By Feven Bishaw

August 07, 2022

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 1 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ተሽከርካሪዎች መንግስት ባወጣው ታሪፍ ብቻ ህብረተሰቡን በሚያገለግሉበት አግባብ ዙሪያ ምክክር ተደርጓል፡፡

ምክክሩ የተደረገው በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሰብሳቢነት፣ ከአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ፣ ከትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ፣ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ አዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን እንዲሁም ከአዲስ አበባ ከንቲባ ፅህፈት ቤት የስራ ሃላፊዎች ጋር በጋራ በመሆን ነው፡፡