አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞንና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን የሚገኙ የየዞኖቹ የሰላም ኮሚቴ አባላት፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች የሚከሰቱ ግጭቶችን ከመሠረቱ ለመፍታት የሚያስችል ውይይት አካሂደዋል።
በደብረብርሃን ከተማ በተካሄደው ውይይት፥ በባለፉት ጊዜያት በተደጋጋሚ እየተከሰተ ባለው ችግር የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞንና የሰሜን ሸዋ ዞን የይፋት ቀጠና ሕዝብ ቀጥተኛ የችግሩ ገፈት ቀማሽ ሆነው ለሰው ሕይወት መጥፋት፣ ለአካል መጉደልና ለንብረት ውድመት መነሻ መሆኑ ተገልጿል፡፡