አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 3 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 1ኛ የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባዔውን እያካሄደ ነው፡፡
ምክር ቤቱ ÷ የአስፈጻሚ አካላት የአፈጻጸም ሪፖርት፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የዋና ኦዲተር ሪፖርቶችን እንዲሁም የክልሉን መንግሥት የ2015 ዓመት የሥራ ዕቅድ፣ ረቂቅ በጀት እና ሌሎች አዋጆችን መርምሮ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል፡፡