ቢዝነስ

ለአምራች ኢንተርፕራይዞች ከ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ የስራ ማስኬጃ ብድር ለማቅረብ ታቅዷል – የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት

By Feven Bishaw

August 09, 2022

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 3 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2015 በጀት ዓመት  ለአምራችኢንተርፕራይዞች 1 ነጥብ 66 ቢሊየን ብር የስራ ማስኬጃ ብድር ለማሰራጨት መታቀዱን የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አስታወቀ፡፡

የአምራች ኢንተርፕራይዞችን የፋይናንስ አቅርቦት ለማሳደግና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ታልሞ በተያዘው እቅድ በባንኮችና በማይክሮ ፋይናንስ አማካኝነት 1 ሺህ 591 ለሚሆኑ አምራችኢንተርፕራይዞች 1 ነጥብ 66 ቢሊየን ብር የስራ ማስኬጃ ብድር ለማሰራጨት የታቀደው፡፡