አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የሚኖሩ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላትና ምሁራን 15 ሺህ መጻሕፍትን ለአብርሆት ቤተ-መጻሕፍትና ለሦስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ድጋፍ አደረጉ፡፡
ድጋፉን ያደረጉትበተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የሚኖሩ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላት በተለይም በአቡዳቢና አካባቢው የሚኖሩ ምሁራን ሲሆኑ÷ መጻሕፍቱ ለአብርሆት ቤተ መጻህፍትና ለወሎ፣ ወልዲያና መዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲዎች መማሪያና ማጣቀሻ እንዲሆኑ ተበርክተዋል፡፡