የሀገር ውስጥ ዜና

የሳይበር ደኅንነት ምርምር ለማካሄድ ስምምነት ተፈረመ

By ዮሐንስ ደርበው

August 10, 2022

የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ እና የዩኒቨርሲቲዎቹ የሥራ ኃላፊዎች ናቸው ስምምነቱን የተፈራረሙት፡፡

ስምምነቱን የተፈራረሙት ዩኒቨርሲቲዎችም÷ ጎንደር፣ ሀዋሳ፣ አርባምንጭ፣ ባሕርዳር፣ ሐረማያ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች መሆናቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ስምምነቱ በአቅም ግንባታና ተሰጥኦ ልማት ዙሪያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል።