የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ እና የዩኒቨርሲቲዎቹ የሥራ ኃላፊዎች ናቸው ስምምነቱን የተፈራረሙት፡፡
ስምምነቱን የተፈራረሙት ዩኒቨርሲቲዎችም÷ ጎንደር፣ ሀዋሳ፣ አርባምንጭ፣ ባሕርዳር፣ ሐረማያ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች መሆናቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ስምምነቱ በአቅም ግንባታና ተሰጥኦ ልማት ዙሪያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል።