የሀገር ውስጥ ዜና

የሕዳሴ ግድብ ሶስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት ተጠናቀቀ

By Feven Bishaw

August 12, 2022

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 6 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሶስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት ተጠናቀቀ፡፡

የክረምት ወቅት መግባትን ተከትሎ ለሶስተኛ ጊዜ ሲካሄድ የቆየው የግድቡ የውሃ ሙሌት በስኬት ተጠናቆ በአሁኑ ወቅት ውሃው በግድቡ አናት ላይ መፍሰስ መጀመሩ ተገልጿል፡፡

በውሃ ሙሌት መጠናቀቅ ማብሰሪያው ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣሕለወርቅ ዘውዴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡