አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 6 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ አንድ የራይድ አሽከርካሪን የገደሉ ጓደኛማቾች በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት መቀጣታቸው ተገለፀ፡፡
1ኛ ተከሳሽ የአብስራ ሰለሞን እና 2ኛ ተከሳሽ በላይነው ንጉስ ካልተያዘው ግብረ-አበራቸው ጋር በመሆን ነሕሴ 6 ቀን 2012 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡30 ሰዓት ራይድ ጠርተው አሽከርካሪውን በንፋስ ስልክ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ክልል የሰዎች እንቅስቃሴ ወደማይበዛበት ገባ ያለ ቦታ ጠርተውት ሆራ ትራዲንግ ተብሎ የሚጠራው ስፍራ ሲደርሱ 2ኛ ተከሳሽ እና ያለተያዘው ሌላ ግብረ-አበራቸው አሽከርካሪ ንጉስ ከፍያለውን አንገቱን አንቀው በመያዝ ወንበር ስር ማስተኛታቸው ተገልጿል፡፡