የሀገር ውስጥ ዜና

በበዓላት የመሠረታዊ ፍጆታ አቅርቦትና ስርጭት ላይ በልዩ ትኩረት ይሰራል – ሚኒስቴሩ

By Feven Bishaw

August 12, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲሱ ዓመት የሕዝብ በዓላት ወቅት የመሠረታዊ ፍጆታ ሸቀጦች አቅርቦትና ስርጭትን ለማሻሻል በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ከክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊዎች ጋር በበዓላት ወቅት የመሠረታዊ ፍጆታ ሸቀጦች አቅርቦትና ስርጭት አፈጻጸም በሚሻሻልበት ጉዳይ ላይ ተወያይቷል፡፡