ስፓርት

በሻምፒዮናው 3ኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው የአትሌቲክስ ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ

By Feven Bishaw

August 12, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑካን ቡድን ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገባ፡፡

በኮሎምቢያ ካሊ በተካሄደው የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው የልዑካን ቡድኑ÷ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ አቀባበል ተደርጎለታል፡፡