Fana: At a Speed of Life!

በግብጽ በእሳት አደጋ የ41 ሠዎች ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 8 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በግብጽ በቤተክርስቲያን ውስጥ በተነሳ የእሳት አደጋ የ41 ሠዎች ህይወት ማለፉ ተሰማ።

በቤተክርስቲያኑ ውስጥ 5 ሺህ ምዕመናን የሰንበት ቅዳሴ እያስቀደሱ እንደነበር የቢቢሲ ዘገባ ያመላክታል።

በጊዛ በሚገኘው አቡ ሰፊን ቤተክርስቲያን እሳት አደጋ ለህልፈት ከተዳረጉት በተጨማሪ በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውም ነው የተሰማው።

የአደጋው መንስኤ ከኤሌክትሪክ ጋር የተያያዘ ሳይሆን እንደማይቀር ፖሊስ አስታውቋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.