Fana: At a Speed of Life!

የአሜሪካ ኮንግረስ አባላት ለጉብኝት ታይዋን ገቡ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት የአሜሪካ ኮንግረስ ልዑካን ቡድን ለሁለት ቀናት ጉብኝት ታይዋን መግባታቸው ተገለጸ።

የአሜሪካ ኮንግረስ ሕግ አውጪ አባላት ታይዋን የገቡት፥ የአሜሬካ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን ከጎበኙ ሁለት ሣምንታት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

በታይዋን ዋና ከተማ ታይፔይ የሚደረገውን የልዑካኑን ጉብኝት ይፋ ያደረገው ደሴቲቱን እንደ ራስ-ገዝ አስተዳደር ቆጥሮ እንደ አሜሪካ ኤምባሲ የሚንቀሳቀስ ተቋም ነው ተብሏል፡፡

እንደ ተቋሙ መረጃ ዴሞክራቱ የማሳቹሴትስ ሴናተር ኤድ ማርኬይ ልዑካን ቡድኑን መርተው ታይዋን ገብተዋል።

በጉብኝቱ የዴሞክራቶቹ ተወካይ የሆኑት ÷ ጆን ጋራሜንዲ እና አለን ሎዌንታል ከካሊፎርኒያ እንዲሁም ዶን ቤየር ከቨርጂኒያ ከቡድን መሪው ጋር በታይፔይ ተገኝተዋልም ነው የተባለው፡፡

በተጨማሪ ከሪፐብሊካኑ ወገን ደግሞ አሙአ አማታ ኮልማን ራዴዋገን ከሳሞአ በመርሐ-ግብሩ ላይ ተሳታፊ መሆናቸውን አር ቲ ዘግቧል፡፡

ልዑካን ቡድኑ ከታይዋን መሪዎች ጋር በቀጣይ በሚኖራቸው ግንኙነት ዙሪያ እንደሚመክሩ ኢንስቲቲዩቱ ገልጿል።

በቀጠናዊ ደኅንነት፣ በንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ በዓለምአቀፍ የአቅርቦት ሰንሰለቶች፣ በዓየር ንብረት ለውጥ እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ እንደሚወያዩም ነው የተመለከተው፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.