አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ድጋፍ ላደረጉ አካላት የምስጋና ዝግጅት እና የኢትዮጵያ ባህል ማስተዋወቂያ መድረክ በጃፓን ካናጋዋ ግዛት በማቺዳ ከተማ ተካሄደ።
በዝግጅቱ በክብር እንግድነት የተገኙት አምባሳደር ተፈራ ደርበው÷ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሦስተኛው የውሃ ሙሌት እንዲጠናቀቅና የሁለተኛው ተርባይን አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።