አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴ ለሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ለተከሰተው ግጭት ሰላማዊ እልባት ለመስጠት ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት ሊያደርስ የሚችል እና ለቀጣይ የፖለቲካ ውይይቶች መሰረት የሚጥል የሰላም ምክረ ሃሳብ ሰነድን አፀደቀ።
የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ÷መንግስት በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል የተከሰተውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ እልባት ለመስጠት የጀመረውን ጥረት ከዳር ለማድረስ የተቋቋመው የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴ እስካሁን የነበረውን እንቅስቃሴ አስመልክቶ መወያየቱን አስታውቋል፡፡