አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በኢሺ ፕሮግራም በጋምቤላ ከተማ ለሚገኘው ኦፔኖ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 30 ሚሊየን ብር የሚገመት ለአይሲቲ መሠረተ ልማት የሚሆኑ የተለያዩ ቁሳቁሶች ድጋፍ አድርጓል።
የኮሌጁ አስተዳደር ምክትል ዲን አቶ ጊል ማንጎግ እንዳሉት÷ የተደረገው ድጋፍ የኮሌጁን የቴክኖሎጂ ሽግግር አቅም በማሳደግና ወጭ በመቀነስ የሥልጠና ጥራትን ለማስጠበቅና የአገልግሎት አሠጣጥን ለማዘመን ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ።