አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኒውዚላንድ አውሎነፋስ የቀላቀለ ወቅቱን ያልጠበቀ ከባድ ዝናብ ያስከተለው “አስፈሪ ጎርፍ” በመቶዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችን ከቄያቸው ማፈናቀሉ ተነገረ፡፡
ለሶስት ተከታታይ ቀን የዘነበ ከባድ ዝናብ የኒውዚላንድ ደቡባዊ ደሴትን ምዕራባዊ እና ሰሜናዊ ክፍል በጎርፍ በማጥለቅለቅ በመቶዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ ሲያስገድድ፥ የመንገድ እና የትምህርት ተቋማት መዘጋት እንዲሁም የመሬት መንሸራተት አስከትሏል።