አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለሀገር ግንባታና የሕዝቦችን ትስስር ለማጠናከር የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በኃላፊነት መስራት እንደሚጠበቅባቸው የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ታዬ ደንደአ ተናገሩ።
የሰላም ሚኒስቴር ከቅን ልቦች በጎ ስራ ድርጅት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው መድረክ “ማህበራዊ ሚዲያ ለሰላም ግንባታ” በሚል መሪ ሀሳብ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የተውጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው።