ቢዝነስ

በባለልዩ ጣዕም የቡና ቅምሻ አንድ ኪሎ የኢትዮጵያ ቡና በ47 ሺህ 236 ብር ተሸጠ

By ዮሐንስ ደርበው

August 24, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ለሦስተኛ ጊዜ ሲካሄድ የቆየው የባለልዩ ጣዕም የቡና ቅምሻ (ካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ) ውድድር የኢትዮጵያ ቡና አሸነፈ፡፡

የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን “ቡናችን ዳግም አሸነፈ፤ አርሶ አደሮቻችንም አሸንፈው የኢትዮጵያ ኩራት ሆነዋል” ብሏል፡፡