ስፓርት

ሊዲያ ታፈሰ ለዓለም ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ውድድር ጥሪ ቀረበላት

By ዮሐንስ ደርበው

August 30, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ በህንድ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የዓለም ሴቶች ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ውድድር ላይ አገልግሎት እንድትሰጥ በፊፋ ጥሪ ቀረበላት፡፡

የዓለም ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ዋንጫ ጨዋታ ውድድር ከጥቅምት 1 እስከ ጥቅምት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በህንድ አስተናጋጅነት ይካሄዳል፡፡