የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያውያን የአንድነት እና መከባበር እሴቶቻቸውን ሊያስጠብቁ ይገባል- የአዲስ አበባ ነዋሪዎች

By Tibebu Kebede

October 31, 2019

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 19 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ከዚህ ቀደም የነበሩትን የአንድነት እና መከባበር እሴቶች ሊያስጠብቁ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

አሁን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተፈጠሩ አለመረጋጋቶችም በፍጥነት እንዲቆሙ መንግስት ህግ የማስከበር ስራ ሊሰራ እንደሚገባም አስተያየት ሰጭዎቹ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።