የሀገር ውስጥ ዜና

በትግራይ ክልል የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በም/ር መስተዳድር የሚመራ ኮሚቴ ተቋቋመ

By Tibebu Kebede

March 16, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7፣2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በትግራይ ክልል የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር የሚመራ ኮሚቴ መቋቋሙን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ምክትል ሃላፊ ዶክተር ፀጋይ በሪሁ÷ የኮሮና ቫይረስ ከቀን ወደ ቀን ስፋቱ እየጨመረ በመምጣቱ የዓለም ስጋት መሆኑን ነው ያነሱት።