የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያን ትንሣኤ ከማረጋገጥ ሊያስቆመን የሚችል አንዳች ምድራዊ ኃይል አይኖርም – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

By Feven Bishaw

September 01, 2022

 

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያን ትንሣኤ ከማረጋገጥ ሊያስቆመን የሚችል አንዳች ምድራዊ ኃይል አይኖርም ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አቀፍ የሻዴይ፣ አሸንድዬና ሶለል በዓልን ልጃገረዶች፥ ወጣቶችና ሴቶች ባከበሩበት ወቅት አሸባሪው የህወሓት ቡድን በኢትዮጵያ ላይ የፈፀመውን ወረራ የሚያወግዝና ለጀግናው መከላከያ ሠራዊት የድጋፍ ንቅናቄ መርሐ ግብር አካሂደዋል፡፡