ስፓርት

በሀገር ውስጥ የሚካሄዱ ስፖርታዊ ውድድሮች እና ጨዋታዎች ለ15 ቀናት እንዳይካሄዱ ተወሰነ

By Tibebu Kebede

March 16, 2020

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 7 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በሀገር ውስጥ የሚካሄዱ ስፖርታዊ ውድድሮች፣ ጨዋታዎች፣ የስፖርት ፌስቲቫል፣ ስልጠናዎች፣ ጉባኤዎች እና ትላልቅ ስብሰባዎች ለ15 ቀናት በየትኛውም ቦታ እንደማይካሄዱ አስታወቀ።

ከዚህ በተጨማሪም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ውድድሮች እና የስልጠና መድረኮች ለህዝቡ ደህንነት ሲባል በቫይረሱ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ በመንግስት እስከሚሰጥ ድረስ እንደማትሳተፍም አስታውቋል።

ከዛሬ ጀምሮም በመንግስት አስፈላጊው መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ምንም ዓይነት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደማይቻል መግለጹን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በኮሚሸኑ አዘጋጅነት በማህበረሰብ ስፖርት ተሳትፎ እና በስፖርታዊ ጨዋነት ማስፈን ዙሪያ መጋቢት 9 እና 10 ቀን 2012 ዓ.ም ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው የባለድርሻ አካላት መድረክ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙም ተገልጿል።

 

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision