አዲስ አበባ፣ ነሐሴ፣ 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰላም ያለው ጽኑ አቋም የሚደገፍ መሆኑን በእስራኤል የመከላከያ ሠራዊት የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊ ኮሎኔል አቪዜር ሴጋል ተናገሩ፡፡
በእስራኤል የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ረታ ዓለሙ ከእስራኤል የመከላከያ ሠራዊት የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊ ከሆኑት ኮለኔል አቪዜር ሴጋል እና ረዳታቸው ጋር በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ተወያይተዋል።