አዲስ አበባ፣ ነሐሴ፣ 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በክልሉ ከሚገኙ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና አባገዳዎች ጋር ተወያይቷል፡፡
በውይይቱ የብልጽግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጃፈር ሱፊያን÷አሸባሪው ህወሓት በተደጋጋሚ የቀረበለትን የሰላም ጥሪ ወደ ጎን በመተው ለሦስተኛ ጊዜ ጦርነት መክፈቱን አስታውሰዋል፡፡