አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እና የስዊዘርላንድን የቆየ ሁለትዮሽ ግንኙነትና ትብብርን በአዳዲስ የተመረጡ መስኮች ለማሳደግ የሚያስችል የጋራ የፖለቲካ ምክክር በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡
በምክክሩ ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ÷ በተለይም በንግድ፣ በልማት ትብብርና በሰብዓዊ ድጋፍ ረገድ ስዊዘርላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት አድንቀዋል፡፡