የሀገር ውስጥ ዜና

ለጥምር ጦሩ እየተደረገ ያለው ድጋፍ ለሠራዊቱ አቅም እና ብርታት ፈጥሯል- ሜ/ ጄነራል ጥሩዬ አሰፌ

By ዮሐንስ ደርበው

September 09, 2022

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በወሎ ግንባር ለሚገኘው ጥምር ጦር እየተደረገ ያለው ድጋፍ ለሠራዊቱ ታላቅ አቅም እና ብርታት እንደፈጠረለት የወሎ ግንባር ሎጂስቲክስ ኃላፊ ሜጀር ጄነራል ጥሩዬ አሰፌ ተናገሩ።

የደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር በግንባር እየተፋለመ ለሚገኘው ጥምር ጦር የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ 22 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ግምት ያለው የአይነት ድጋፍ አድርጓል፡፡