የሀገር ውስጥ ዜና

ከአሸባሪው ትህነግ ተልዕኮ ተቀብለው የህዝብን ሰላም ሲያውኩ የነበሩ 19 የሽብር ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ

By Feven Bishaw

September 09, 2022

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከአሸባሪው ትህነግ ተልዕኮ ተቀብለው በአዲስ አበባ እና አካባቢው የህዝብን ሰላም ሲያውኩ የነበሩ 19 የሽብር ቡድን አባላት በተደረገው ከፍተኛ ዘመቻ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ፡፡

ጠላቶች አዲስ አበባን የሽብር ማዕከል እናደርጋለን ብለው በአደባባይ ከፎከሩበት ጊዜ ጀምሮ እኩይ ተግባራቸውን ለመፈፀም ያላደረጉት ሙከራ እንዳልነበረ የቅርብ ጊዜ ትውስታ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል፡፡