የሀገር ውስጥ ዜና

የደብረታቦርን የውኃ ችግር ለመፍታት የማስፋፊያ ፕሮጀክት እየተሠራ ነው

By ዮሐንስ ደርበው

September 13, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የደብረታቦር ከተማን የውኃ ችግር ለመፍታት በ134 ሚሊየን ብር የማስፋፊያ ፕሮጀክት እየተሠራ መሆኑን የአማራ ክልል ውኃና ኢነርጂ ቢሮ አስታወቀ፡፡

የቢሮው ኃላፊ ዶክተር ማማሩ አያሌው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ በከተሞች የሚታየውን የውኃ አገልግሎት ችግር ለማስተካከል ቢሮው የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ ነው።