አየር መንገዱ ባለ 5 ኮከብ ሆቴል ከፈተ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል መክፈቱን አስታወቀ፡፡
ሆቴሉ ከመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል -ሁለት ጋር የተገናኘና ለመሳፈሪያ በሮችም ቅርብ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የሆቴሉ ግንባታ በፈረንጆቹ 2020 ታህሳስ ወር ላይ የተጀመረ ሲሆን ÷ ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ ተመላክቷል፡፡
ሆቴሉ በውስጡ 41 የእንግዳ ማረፊያ ክፍሎች እንዳሉትም ነው የተገለጸው፡፡
ሆቴሉ በስካይላይት ሆቴል ሥር የሚተዳደር መሆኑንም ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።