የሀገር ውስጥ ዜና

የጎርፍ አደጋ የእናትና ልጅን ሕይወት ቀጠፈ

By ዮሐንስ ደርበው

September 14, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰሜን ሸዋ ዞን መርሐቤቴ ወረዳ እናትና ልጅ ወንዝ ሲያቋርጡ በጎርፍ አደጋ ህይወታቸው ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ።

እናትና ልጅ በወረዳው ኮራ ወንጭት ቀበሌ ደብረ ወግሽ አካባቢ ነዋሪ መሆናቸው ታውቋል።