አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ህብረተሰቡ ከሕጋዊ አሠራር ውጪ ማህበር እናደራጃለን፣ ቀረጥና ታክስ ነጻ አስፈቅደናል ወይም እናስፈቅዳለን ከሚሉ አካላት እንዲጠነቀቅ ገንዘብ ሚኒስቴር አሳስቧል፡፡
ሚኒስቴሩ በሰጠው ማብራሪያ በመዲናዋ በማገልገል ላይ የሚገኙ የላዳ ታክሲዎች በአዲስ እንዲተኩ በማድረግ ባለንብረቶቹን በተሽከርካሪዎቹ እርጅና ምክንያት ከሚደርስባቸው ከፍተኛ የነዳጅና የመለዋወጫ ወጪ ለማዳን አዳዲስ ተሽከርካሪዎች ከቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆኑ መደረጉን አስታውሷል።