የሀገር ውስጥ ዜና

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በከፊል ሊዘጉ ነው

By Tibebu Kebede

March 18, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ በከፊል እንደሚዘጉ የጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ።

የጠቅላይ ፍርድቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ በሰጡት መግለጫ ፍርድቤቶች ከመጋቢት 10 እስከ መጋቢት 24 የሚዘጉ ሲሆን በዚህም ጊዜ አዳዲስ መዝገቦች አይከፈቱም ብለዋል።