Fana: At a Speed of Life!

በሲድኒ  የሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውስትራሊያ ሲድኒ በተደረገ የሴቶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵውያን አትሌቶች በፍጽም የበላይነት አሸንፈዋል፡፡

አትሌት ትዕግስት ግርማ ርቀቱን 2 ሰዓት 25 ደቂቃ ከ10 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመጨረስ  ወድድሩን በአንደኛነት አጠናቃለች፡፡

ሌላኛው ኢትዮጵያዊ  አትሌት  ለተብርሃን ሀይላይ ርቀቱን  2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ 45 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመጨረስ ሁለተኛ ስትሆን ÷ኤርትራዊቷ ናዝሬት ወልዱ ደግሞ ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች።

በውድድሩ ኢትዮጵያውን አትሌቶች ከ1 እስከ 2 እና ከ4 እስከ 6 ያለውን ደረጃ በመያዝ ነው በፍጹም የበላይነት ያሸነፉት፡፡

በተመሳሳይ በወንዶች የሲድኒ ማራቶን ደግሞ ኢትዮጵያዊው አትሌት ጫሉ ዲሶ  ርቀቱን 2 ሰዓት ከ07 ደቂቃ ከ09 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመግባት ሦስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡

እጅግ ከባድ ፉክክር በታየበት በሲድኒ የወንዶች ማራቶንን ኬንያዊው ሞሰስ ኪቤት ማሸነፉን ከሲድኒ ኦሎምፒክ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.