የሀገር ውስጥ ዜና

መንግስት የዓለም አቀፉ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ባለሙያዎች ኢትዮጵያን በተመለከተ ያወጡትን ሪፖርት ውድቅ አደረገ

By ዮሐንስ ደርበው

September 21, 2022

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 11 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም አቀፉ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ባለሙያዎች ኢትዮጵያን በተመለከተ ያወጡት ሪፖርት የፖለቲካ አጀንዳ ለመፍጠር ታልሞ የተሰራ ነው ሲል ውድቅ አድርጎታል።

ቡድኑ ላለፉት 10 ወራት በኢትዮጵያ ተፈፅመዋል የተባሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ከዓለም አቀፍ ህግ እና ከስደተኛ ህጎች አንፃር አጣራለሁ ብሎ ሲሰራ ቆይቷል።