የሀገር ውስጥ ዜና

የደቡብ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት 93 ፕሮጄክቶችን መርምሮ አፀደቀ

By Feven Bishaw

September 22, 2022

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 12 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ዛሬ ባካሔደው መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ የኢንቨስትመንት ፕሮጄክቶች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ።

መስተዳድር ምክር ቤቱ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ እና በአገልግሎት ዘርፍ የቀረቡ 93 ፕሮጄክቶችን መርምሮ እንዲጸድቁ ውሳኔ ማሳለፉን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡