የሀገር ውስጥ ዜና

20 ሜጋ ዋት የከርሰምድር እንፋሎት ኃይል መገኘቱ ተገለጸ

By ዮሐንስ ደርበው

September 23, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከአሉቶ ላንጋኖ ጥልቅ የከርሰ ምድር እንፋሎት ቁፋሮ ፕሮጀክት እስካሁን 20 ሜጋ ዋት የሚደርስ የእንፋሎት ኃይል መገኘቱ ተገለጸ፡፡

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሉቶ ጂኦተርማል ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ መሳይ ፍቃዱ እንደገለፁት÷ እስካሁን ቁፋሯቸው ከተጠናቀቀና የምርት ፍተሻ ከተደረገላቸው አምስት ጥልቅ ጉድጓዶች መካከል በአራቱ 20 ሜጋ ዋት የእንፋሎት ኃይል ተገኝቷል፡፡