የሀገር ውስጥ ዜና

አርሶአደሩ የመስኖ ግድቦችን በስፋት መጠቀም አለበት – ዶ/ር ይልቃል ከፋለ

By ዮሐንስ ደርበው

September 25, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በየአካባቢው ያለ አርሶአደር ትንንሽ ግድቦች እና በቀጣይ ወደሥራ የሚገቡትን ትላልቅ ግድቦች በመጠቀም በመስኖ ልማት ላይ በስፋት መሳተፍ እንዳለበት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ ተናገሩ፡፡

አርሶ አደሮች የበጋ የመስኖ ስንዴ ልማትን ከድህነት መውጫ መንገድ ሊያደርጉት እንደሚገባም በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡