የሀገር ውስጥ ዜና

ስደትን ለመከላከል ለወጣቶች አማራጭ የሥራ እድል መፍጠር እንደሚገባ ተጠቆመ

By ዮሐንስ ደርበው

September 25, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሕገወጥ የሰዎች ዝዉዉርና ስደትን ለመከላከል ለወጣቶች አማራጭ የሥራ እድል መፍጠር ተገቢ ነው ተባለ፡፡

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ጂማ ዲልቦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጂቶች በሀገር ዕድገት ላይ ያላቸዉን ሚና መጠቀም ይገባል ሲሉ ተናግረዋል፡፡