የሀገር ውስጥ ዜና

ታላቁ የህዳሴ ግድብ የቱሪዝም እንቅስቃሴን በከፍተኛ ደረጃ የሚያነቃቃ ፕሮጀክት ነው- አቶ አሻድሊ ሀሰን

By ዮሐንስ ደርበው

September 25, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከኃይል ማመንጫነት ባሻገር የቱሪዝም እንቅስቃሴን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ፕሮጀክት መሆኑን የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ገለጹ፡፡

አቶ አሻድሊ ሀሰን፣ የየቱሪዝም ሚኒስትሯ ናሲሴ ጫሊን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች 35ኛውን የዓለም የቱሪዝም ቀን ምክንያት በማድረግ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ትናንት ጎብኝተዋል፡፡