የሀገር ውስጥ ዜና

በዓሉን ስናከብር አካባቢያችንን ከሰርጎ ገቦች በመጠበቅ መሆን አለበት- የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር

By ዮሐንስ ደርበው

September 26, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የደመራና መስቀል በዓልን ስናከብር አካባቢያችንን ለጥፋት ከተሰለፉ ሰርጎገቦች በመጠበቅ ሊሆን ይገባል ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ተናገሩ፡፡

አቶ ማስረሻ በላቸው ለክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡