የሀገር ውስጥ ዜና

10ኛው የጣና ፎረም ጉባዔ ለባሕርዳር ከተማ ገፅታ ግንባታ ልዩ ቦታ ይሰጠዋል- አቶ ጣሂር ሙሃመድ

By ዮሐንስ ደርበው

September 29, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በባሕርዳር ከተማ የሚካሄደው 10ኛው የጣና ፎረም ጉባዔ ለከተማዋ ቱሪዝም ዕድገትና ገፅታ ግንባታ ልዩ ቦታ እንደሚሰጠው የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ጣሂር ሙሃመድ ተናገሩ፡፡

አቶ ጣሂር ከጣና ፎረሙ ጉባዔ መካሄድ ጋር በተያያዘ በሰጡት መግለጫ÷ ጉባዔው ከጥቅምት 4 እስከ 6 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚካሄድ ገልጸዋል፡፡