Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የ11 ሀገራት አምባሳደሮችን የሹመት ደብዳቤ ተቀበሉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በጽህፈት ቤታቸው በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙ የ11 ሀገራት አምባሳደሮችን የሹመት ደብዳቤ ተቀበሉ።

አምባሳደሮቸ የኢራን ፣ ቤልጂየም ፣ ኖርዌይ ፣ ኒጀር ፣ ኦስትሪያ ፣ ብራዚል፣ ኩዌት ፣ ሳኡዲ አረቢያ ፣ ፓርቹጋል ፣ ሲንጋፓር እና ዶሚኒካን ሪፐብሊክ ናቸው።

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ የሹመት ደብዳቤ ካቀረቡ አምባሳደሮች ጋር በኢትዮጵያ እና በሀገራቱ መካከል ያሉ ግንኙነቶችን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.