የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ ሞሀሙድ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመለሱ

By ዮሐንስ ደርበው

September 30, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉት የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ ሞሀሙድ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው ለፕሬዚዳንቱ ሽኝት አድርገዋል ።