አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 216 የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰዱን የደቡብ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ሃላፊ ወይዘሮ ሂክማ ከይረዲን በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ፥ የኮሮና ቫይረስ ወደ ሀገሪቱ መግባቱን ተከትሎ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ መስተዋሉን ተናግረዋል።