የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የቴሌኮም ኅብረት ጋር ያላትን ትብብር እንደምታጠናክር ገለጸች

By ዮሐንስ ደርበው

October 03, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የቴሌኮም ኅብረት ጋር ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና በስዊዘርላንድ የኢትዮጵያ ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ዘነበ ከበደ ተናገሩ፡፡

የዓለም አቀፉ የቴሌኮም ኅብረት በሮማኒያ ቡካሬስት ባካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ÷ ድርጅቱን በቴሌኮሙኒኬሽን ልማት ቢሮ ዳይሬክተርነት ሲያገለግሉ የነበሩትን ዶረን ቦግዳንን ዋና ጸሐፊ አድርጎ መርጧል።