አዲስ አበባ፣ መስከረም 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጥቅምት ወር የመጀመሪያዎቹ አሥር ቀናት በአብዛኛው በደቡብና በምዕራብ አጋማሽ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የተሻለ የእርጥበት ገጽታ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
የመኸር ሰብል አምራች በሆኑትም ሆነ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎች የእርጥበት ሁኔታው ከቀደመው አንጻር ሲታይ ከሞላ ጎደል ጥንካሬ እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡